-ከ80 የሚበልጡ ስደተኞች ሜድትራኒያን ባሕር ዉስጥ ሰምጠዉ ሳይሞቱ እንዳልቀረ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አስታወቀ።ዓለም አቀፉ የፍልስተኞች ጉዳይ ድርጅት (IOM) እንደሚለለዉ 120 ስደተኞች አሳፍራ ከሊቢያ ወደ አዉሮጳ ትቀዝፍ የነበረች አነስተኛ ጀልባ ባለፈዉ ዕሁድ ሰጥማለች።32ቱ በሕይወት ተርፈዋል።-----የእስራኤል-ዩናይትድ ስቴትስና የኢራን ጦር ኃይላት አንዳቸዉ የሌላዉን ተቋማትና ይዞታዎች በደብደባቸዉን ዛሬም እንደቀጠሉ ነዉ።የቃላት ጦርነቱም እንደናረ ነዉ።---ጦርነቱ የእርዳታ ምግብ፣መድሐኒትና ቁሳቁስ እንዳይንቀሳቀስ ወይም እንዲዘገይ ማድረጉን የተባበሩት መንግሥታት ድርጅቶች አስታወቁ።