የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በኻርቱም የሚገኝ የአምባሳደሯ መኖሪያ ቤት በወታደራዊ አውሮፕላን ተደብድቧል በሚል ያቀረበችውን ክስ የሱዳን ጦር አስተባበለ። በደቡብ አፍሪካ ምሥራቅ ኬፕ ክፍለ ግዛት በተፈጸመ ጥቃት የተገደሉ ሰዎች ቁጥር ወደ 18 አሻቀበ። ርዋንዳ ኃይለኛ ተላላፊ በሆነው ኢቦላ መሰል የማርበርግ ቫይረስ ወረርሽኝ ስምንት ሰዎች መሞታቸውን አስታወቀች። እስራኤል ሊባኖስን በእግረኛ ወታደሮች ከወረረች ሒዝቦላሕ ለውጊያ ዝግጁ መሆኑን አስታወቀ። የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር ዮቭ ጋላንት ሀገራቸው እግረኛ ወታደሮቿን ወደ ሊባኖስ ልታዘምት እንደምትችል ፍንጭ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ ኢራንን አስጠንቅቀዋል