ዜና መጽሔት

የመስከረም 20 ቀን 2017 የዜና መጽሔት


Listen Later

የዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ግጭቶች በሰላማዊ መንገድ እንዲፈቱ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ለመተባበር ቁርጠኛ ሆና እንደምትቀጥል በኢትዮጵያ የአሜሪካው አምባሳደር ተናገሩ። ኤርትራን ጨምሮ ከሌሎች ሁሉም አጎራባች ህዝቦች ጋር ዘላቂ ሰላም ለመፍጠር እንደሚሰሩ የትግራይ ግዚያዊ አስተዳደር ፕሬዝደንት አቶ ጌታቸው ረዳ ገለፁ። በሆሮ ጉዱሩ ወለጋ ዞን አሙሩ ወረዳ የጸጥታ ሀይሎችን ጨምሮ ስድስት ሰዎች ያለፈው ቅዳሜ በታጣቂዎች መገደላቸውን የአካባቢው ነዋሪዎች ተናግረዋል፡፡ ጥራታቸውን ሳይጠብቁ ወደ ውጪ የሚላኩ ቡናዎች ኢትዮጵያ ከዘርፉ ተገቢውን ገቢ እንዳታገኝ ማድረጉን የኢትዮጵያ ቡና እና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ፡፡
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

ዜና መጽሔትBy DW