የአርቲስት ቴዎድሮስ ካሣሁን ስቱዲዮ መዘረፉን የአርቲስቱ የቅርብ ሰው ለዶቼ ቬለ አረጋገጡ። በሶማሊያ በተከሰተው ድርቅ በ 5 ወረዳዎች ብቻ ወደ 62,000 የሚጠጉ ሶማሊያውያን መፈናቀላቸውን የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ጉዳይ ድርጅት አስታወቀ። እስራኤልና ሊባኖስ ከዚህ ቀደም የደረሱት የተኩስ አቁም ስምምነት ለሦስት ሳምንታት ማራዘማቸውን የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ አስታወቁ። የኢራኑ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አባስ አራግቺ ማምሻውን ወደ ኢዝላማባድ እንደሚገቡ ኢራን አረጋገጠች።