በዋግ ህምራ ብሄረሰብ አስተዳደር ዞን፣ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ20 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ፣ በ62 ሰዎች ላይ ደግሞ ከባድ እና ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱ ተገለጸ። በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ ከተማ ሦስት ኢትዮጵያዊያን በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን ታውቋል። ኢትዮጵያዊያኑ ትናንት የተገደሉት በአንድ ምግቤት ውስጥ በመመገብ ላይ እንዳሉ ነው ፡፡ባሕሬይን አስፈላጊ ተቋሞቿን ፎቶ በማንሳት ለኢራን አስተላልፏል ያለቻቸውን 5 ሰዎች የዕድሜ ይፍታህ እስር ውሳኔ አስተላለፈች። አሜሪካ፤ ኢራን ያቀረበችው የመደራደሪያ ሐሳብ እያጤነችው መሆኗን አስታወቀች።