የአውሮጳ ሕብረት ትግራይ ክልል ውስጥ ሌላ አውዳሚ ጦርነት ከሚያስከትል እርምጃ ሁሉም ወገኖች እንዲታቀቡ አሳሰበ።
ኢትዮጵያዊን ጨምሮ ዘጠኝ አፍሪቃውያን ስደተኞችን የአሜሪካ መንግሥት ወደ ካሜሮን ማባረሩን ጠበቃቸው ተናገሩ።
የተመድ ዴሞክራቲክ ኮንጎ ኢቱሪ ክፍለ ሀገር ጁጉ ግዛት በደረሰ ጥቃት ምክንያት ወደ 200 ገደማ ነዋሪዎች ተፈናቅለው መጠለያ እንደሚያስፈልጋቸው አመለከተ።
የተመድ የፀጥታው ምክር ቤት ደቡብ ሱዳን ውስጥ ያሰማራውን የሰላም አስከባሪ ኃይል ቁጥር ለመቀነስ ወሰነ። የሰላም አስከባሪውን የቆይታ ጊዜም እስከ መጪው ጎርጎሪዮሳዊ ዓመት 2027 ሚያዝያ 30 ቀን ድረስ አራዝሟል።