በኬንያ ሰሞኑን በጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፋና የመሬት መንሸራተት ቢያንስ 10 ሰዎች ሞቱ። ታይዋን ፕሬዝዳንት ከአፍሪቃ ብቸኛዋ ዲፕሎማሲያዊ አጋር ሀገር ኤስዋቲኒ ገቡ።3,000 የሚጠጉ የየመን ስደተኞች ከዩናይትድ ስቴትስ እንዳይባረሩ አንድ የፌዴራል ዳኛ ከለከሉ። የነዳጅ ዘይት የጫነ አንድ መርከብ ከየመን የባህር ዳርቻ ተጠለፈ። ዩናይትድ ስቴትስ 5000 የሚጠጉ ወታደሮቿን ከጀርመን ልታስወጣ ነው። የአውሮፓ ህብረት እና የጀርመን ኢንዱስትሪዎች የትራምፕን አዲስ የታሪፍ ዕቅዶች ተቹ።የተባበሩት አረብ ኤምሬቶች የአየር ክልሉ ሙሉ በሙሉ ለመደበኛ በረራዎች ክፍት እንደሚሆን አስታወቁ።