የአስራ አራት ሀገራት ኤምባሲዎች “በኢትዮጵያ ሐሳብን የመግለጽ ነጻነት ብርቱ ጫና ውስጥ ሆኖ መቀጠሉ” እንደሚያሳስባቸው ገለጹ። በደቡብ ሱዳን በድሮን ጥቃት ቢያንስ ሰባት ሰዎች መገደላቸውን እና ሌሎች 20 መቁሰላቸውን ድንበር የለሽ የሐኪሞች ቡድን አስታወቀ። የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ድሮኖች ከኤርትራ ድንበር አቅራቢያ የምትገኘው የከሰላ ከተማ ላይ ጥቃት መፈጸማቸውን ወታደራዊ የመረጃ ምንጮች ተናገሩ። ፕሬዝደንት ቭላድሚር ፑቲን ለሦስት ቀናት ተኩስ ለማቆም ላቀረቡት ምክረ-ሐሳብ ዩክሬን ግልጽ ምላሽ እንድትሰጥ ክሬምሊን ጠየቀ። በሻንጋይ ዳይመንድ ሊግ ኢትዮጵያውያኑ ጽጌ ዱጉማ፣ በሪሁ አረጋዊ እና አብርሀም ስሜ አሸናፊ ሆኑ።