የዓለም ዜና

የሚያዝያ 3 ቀን 2018 ዓ.ም የዓለም ዜና


Listen Later

ኢትዮጵያ ውስጥ የከርቤ ዛፍ በድርቅ ምክንያት እየተመናመነ እንደሆነ አሶሺየትድ ፕረስ ዘገበ። የጅቡቲው ፕሬዝደንት ጉሌሕ 97.81% የመራጭ ድምፅ በማግኘት አሸነፉ።
የእስራኤል ጦር ባለፉት 24 ሰዓታት ሊባኖስ ውስጥ ከ200 በላይ የሂዝቦላ ኢላማዎች መደብደቡን አስታወቀ። የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ኃላፊዎች በመካከለኛው ምስራቅ የሚደረግ የአለም አቀፍ ህግ ጥሰት እንዲቆም ጠይቁ። የኢራን እና የዩናይትድ ስቴትስ የፊት ለፊት ድርድር ዛሬ በፓኪስታን ዋና ከተማ ኢስላማባድ ከጥቂት ሰዓታት በፊት ጀምሯል።
ከ50 ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ጨረቃ አቅራቢያ የነበሩት የጠፈር ተመራማሪዎች በሰላም ወደ ምድር ተመለሱ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW