በሱዳን እየተካሄደ ባለው ጦርነት ምክንያት ሱዳናውያን ሕይወታቸውን ለመታደግ ሲሉ ቅጠላ ቅጠልና የእንስሳት መኖ ጭምር ለመመገብ መገደዳቸውን 5 መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች አስታወቁ። በናይጄርያ ሰሜን ምስራቅ በምትገኝ አንዲት መንደር የሐገሪቱ አየር ሃይል በገበያ ቦታ ፈጸመው በተባለው የአየር ድብደባ ቢያንስ 200 ሰላማዊ ሰዎች ሳይሞቱ እንዳልቀረ ተሰግቷል። የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕ የኢራን ወደቦች በሙሉ እንዲዘጉ ትዕዛዝ ማስተላለፋቸውን ተከትሎ ኢራን ፈጣን የዛቻ ምላሽ ሰጥታለች።