አራተኛ ዓመቱን በያዘው የሱዳን የእርስ በእርስ ጦርነት በረሐብ እየተሰቃዩ ያሉ ወገኖችን ለመርዳት ጀርመን 20 ሚልዩን ዩሮ እንደምትለግስ አስታወቀች። አሜሪካ ከኢራን ወደቦች የሚወጡና የሚገቡ መርከቦችን ማገዷን ከቀጠለች በቀይባሕር፣ የፐርሺያ ባሕረሰላጤና በኦማን የባሕር ሰርጥ የሚንቀሳቀሱ የንግድ መርከቦችን እንቅስቃሴ እንደምታግድ ኢራን አስጠነቀቀች። እስራኤል በአለፉት 24 ሰዓታት በደቡብ ሊባኖስ በሚገኙ ከ200 በላይ «የሒዝቦላሕ ወታደራዊ ይዞታዎች» ባለቻቸው ቦታዎች ላይ ጥቃት መፈጸሟን አስታውቃለች።