የዓለም ዜና

የሚያዚያ 10 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

-በመላዉ ዓለም የሚገኙ የክርስትና እምነት ተከታዮች ዛሬ የሥቅለት በዓልን አክብረዉ ዋሉ።በአሉ ቫቲካን ዉስጥ በርዕሰ ሊቃነ-ጳጳሳቱ ሕመም፣ እየሩሳሌም ዉስጥ በጦርነት መሐል ግን የግሪጎሪያንና የዩሊዮስ የቀን አቀጣጠርን በሚከተለዉ ዓለም ሁሉ አንድ ቀን ተከብሯል።----የእስራኤል ጦር ጋዛ ሠርጥ፣ የዩናይትድ ስቴትስ ጦር ደግሞ የመን ዉስጥ በርካታ ሰዎችን ገደሉ።እስራኤል ታጋቾች እንዲለቀቁ ያቀረበችዉን ጥያቄ ሐማስ ዉድቅ አደረገዉ።---የዩክሬንና የሩሲያን ጦርነትን በድርድር ለማስቆም ዩናይትድ ስቴትስ የምታደርገዉ ጥረት ባጭር ጊዜ ዉጤት ካላመጣ ጥረቱን ልታቆም እንደምትችል ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሯ አስታወቁ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW