-የኢትዮጵያ የጤና ባለሙያዎች የደሞዝ ጭማሪ እንዲደረግላቸዉና ጥቅማጥቅሞች እንዲከበሩላቸዉ በየሚሰሩበት ተቋማት በመሠለፍ ጠየቁ።በተለያዩ ሆስፒታሎችና የጤና ተቋማት የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎች ጥያቄያቸዉ ተገቢ መልስ ካላገኘ የሥራ ማቆም አድማ እንደሚመቱ አስጠንቅቀዋል።---ሕንድና ፓኪስታን አዲስ የገጠሙትን ግጭት እንዲያቆሙ የተለያዩ መንግሥታት ጠየቁ።ሁለቱ ኑክሌር የታጠቁ ተጎራባች መንግስታት ግን አንዳቸዉ ሌላቸዉን ለማጥቃት እየተዛዛቱ ነዉ።-ፈረንሳይና ጀርመን ፍራንኮ-ጀርመን የተባለ የመከላከያና የፀጥታ የጋራ ምክር ቤት ለመመሥረት ተስማሙ።