የሚያዚያ 9 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
በዳፍሩርዋ ኤል ፋሸር በተካሄደ ግጭት ቢያንስ 57 ሰላማዊ ሰዎች መገደላቸው ተሰማ።ሰላማዊ ሰዎቹ የተገደሉት የመንግስት ጦርን የሚወጋው ፈጥኖ ደራሹ ኃይል ትናንት በከተማይቱ ባካሄደው ድብደባ ነው።
የሶማሊያና የአሜሪካን ኃይሎች አሸባብ ጥቃት በከፈተበት በአዳን ያባል በጋራ ባካሄዱት የአየር ጥቃትና ውጊያ 12 የቡድኑን ሚሊሽያዎች መግደላቸውን የሶማሊያ መንግስት ዛሬ አስታወቀ።
የዩክሬን ፕሬዝዳንት ቮሎዶሚር ዜሌንስኪ ከፍተኛ አማካሪዎቻቸው በፓሪስ ከአሜሪካና ከአውሮጳውያን ጋር በተነጋገሩበት በዛሬው እለት የዩክሬኑ ጦርነት እንዲቆም ሩስያ ላይ ግፊት እንዲደረግ ጠየቁ።