የቀድሞው የኢትዮጵያ ራድዮ የዜና ፋይል ባልደረባ የነበረው በአሁኑ ሰዓት ደግሞ በአሃዱ ራድዮና በተለያዩ የዩቱብ ቻናሎች የተረክ ሚዛንና ቅዳሜ ገበያ የመሳሰሉ ፕሮግራሞችን በማዘጋጀትና በማቅረብ ላይ የነበረው ጋዜጠኛ አብዱልሰመድ መሀመድና የሪፖርተር ጋዜጣ ባልደረባ ጋዜጠኛ ዮናስ አማረ በጸጥታ ሃይሎች መታሰራቸውን ተዘገበ። እስራኤል በዮርዳኖስ ምዕራባዊ ዳርቻ በሺዎች የሚቆጠሩ ቤቶችን ለመገንባት የያዘችውን ዕቅድ እንድትሰርዝ ፈረንሳይ አሳሰሰበች። የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕና የሩስያው ፕረዚደንት ቭላድሚር ፑቲን የአላስካው ውይይት ያለውጤት መጠናቀቁን ተነገረ።