የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሃይሎች በሰሜን ዳርፉር በሚገኝ አንድ የተፈናቃዮች መጠለያ ጣቢያ በፈጸሙት ጥቃት ቢያንስ 31 ስቪሎች መገደላቸውንና 13 መቁሰላቸውን የሕክምና ምንጮች አስታወቁ። እስራኤል የየመን ሁቲ ዓማፅያን ይጠቀሙበት ነበር ያለችውን የሃይል መሰረተ ልማት ማውደሟን አስታወቀች። የተለያዩ የአውሮፓ ሐገራት መሪዎች፣ የአሜሪካው ፕረዚደንት ዶናልድ ትራምፕና የዩክሬይኑ ፕረዚደንት ቮሎደሚር ዘለንስኪ በዋሽንግተን ዲሲ ነገ በሚያካሂዱት ውይይት ለመሳተፍ እንደሚጓዙ ገለጹ።