የዓለም ዜና

የነሐሴ 15 ቀን 2017 የዓለም ዜና


Listen Later

-የኢትዮጵያ መንግሥት ባለሥልጣናት ያሰሯቸዉን ጋዜጠኞች ያለምንም ቅድመ-ሁኔታ እንዲፈቱ ሁለት ዓለም አቀፍ የጋዜጠኞች ተቆርቋሪ ድርጅቶች ጠየቁ።የጋዜጠኞች መብት ተሟጋቾች እንደሚሉት ኢትዮጵያ ለነፃ ፕረስና ለጋዜጠኝነት ሥራ አደገኛ እየሆነች ነዉ።---የእስራኤል ጦር ሠሜናዊ ጋዛ ዉስጥ የሚሰሩ የሕክምና ባለሙያዎችና የርዳታ ድርጅት ሰራተኞች አካባቢዉን ለቅቀዉ ለመዉጣት እንዲዘጋጁ አሳሰበ።ጦሩ የጋዛ-ከተማን ሙሉ በሙሉ ለማስገበር እየተዘጋጀ ነዉ።---የምዕራባዉያን ሐገራት ጦር ዩክሬን ዉስጥ ይሰፈር የሚለዉን ሐሳብ ሩሲያ አጥብቃ ተቃወመች።የሩሲያ-ዩክሬንን ጦርነት ለማቆም የሚደረገዉ የዲፕሎማሲ ጥረት፣ጦርነቱም እንደቀጠሉ ነዉ።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW