የዓለም ዜና

የነሐሴ 19 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና


Listen Later

የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በዳርፉር 13 ስቪሎችን መግደላቸውን የአካባቢው የሕክምና ምንጮች ተናገሩ። ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ሴቶች እና ሕጻናት ናቸው ተብሏል።
ሴኔጋል አዲስ በኤምፖክስ የተያዘ ሰው ማግኘቷን የሐገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ቫይረሱ ተገኘበት የተባለው ግለሰብ ከሌላ አገር የመጣ የውጭ ዜጋ ነው ብሏል።
እስራኤል ጋዛ ውስጥ በካንዩኑስ በሚገኝ ናስር ሆስፒታል በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 15 ፍልስጤማውያንና 4 ጋዜጠኞች ተገደሉ። ከሞቱት ውስጥ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችም እንደሚገኙባቸው ተነግሯል።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW