የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይሎች በዳርፉር 13 ስቪሎችን መግደላቸውን የአካባቢው የሕክምና ምንጮች ተናገሩ። ከተገደሉት አብዛኛዎቹ ሴቶች እና ሕጻናት ናቸው ተብሏል።
ሴኔጋል አዲስ በኤምፖክስ የተያዘ ሰው ማግኘቷን የሐገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ቫይረሱ ተገኘበት የተባለው ግለሰብ ከሌላ አገር የመጣ የውጭ ዜጋ ነው ብሏል።
እስራኤል ጋዛ ውስጥ በካንዩኑስ በሚገኝ ናስር ሆስፒታል በፈጸመችው ጥቃት ቢያንስ 15 ፍልስጤማውያንና 4 ጋዜጠኞች ተገደሉ። ከሞቱት ውስጥ የአደጋ ጊዜ ሰራተኞችም እንደሚገኙባቸው ተነግሯል።