አርዕሥተ ዜና
-የኮንጎ ዴሞክራቲክ ሪፐብሊክና የሩዋንዳ መንግሥታት የስደተኞች ልዉዉጥ ለማድረግ ተስማሙ።ሁለቱ መንግሥታት የሰላም ስምምነት ቢፈራረሙም ምሥራቃዊ ኮንጎ ዉስጥ ያለዉ ዉጥረት አሁንም እንደቀጠለ ነዉ።---እስራኤል ጋዛ ሰርጥ ላይ የከፈተችዉ ጥቃት እንዲቆም የሚደረገዉ ግፊት፣ ጥሪና ተማፅዕኖ እንቀጠለ ነዉ።የአሜሪካ ፕሬዝደንት ዛሬ ሥለጋዛ የሚነጋገር ሥብሰባ ዋሽግተን ዉስጥ ያስተናግዳሉ።-የጀርመን መንግሥት ብሔራዊ የፀጥታ ምክር ቤት ለመመሥረት ወሰነ።በዩናይትድ ስቴትስና በብሪታንያ የብሔራዊ ደሕንነት ምክር ቤቶች አምሳያ ይዋቀራል የተባለዉ ምክር ቤት የሐገሪቱን የፀጥታ መርሕ ያቀናጃል፣በቀዉስ ጊዜ ፈጣን መልስ ይሰጣል