በትግራይ ክልል ኃይሎችና ራሱን ከትግራይ ኃይሎች ነጥሎ በአፋር ይንቀሳቀሳል በተባለው ቡድን መካከል ተነሳ የተባለው ግጭት ፣ ካለፈው ሐሙስ አንስቶ የህዝብ የመጓጓዣ አገልግሎት መስጫዎች መንቀሳቀስ ማቆማቸው በጎጃም አካባቢዎች ያስከተላቸው ችግሮች ፣ብልጽግና ፓርቲ ባለፈው ሳምንት ያወጣው መግለጫና የተቃዋሚ የፖለቲካ ፓርቲዎች አስተያየት እንዲሁም ፣ ነዳጅ በውድ ዋጋ ለመግዛት ተገደናል የሚሉ ሾፌሮችና የመኪና ባለቤቶች ሮሮ በዛሬው የዜና መጽሔት ዝግጅታችን የሚያስቃኘን ጉዳዮች ናቸው።