-ከኦሮሚያ ክልል ከተለያዩ የወለጋ ዞኖች ተፈናቅለዉ አማራ ክልል የሰፈሩ ሰዎች ለተቃጠለ ቤትና ለማያርሱት መሬት ግብር እንዲከፍሉ መጠየቃቸዉን አስታወቁ።---የሱዳን ወታደራዊ መሪ ጄኔራል አብዱልፈታሕ አል-ቡርሐን ከዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት የአፍሪቃ ጉዳይ ልዩ አማካሪ ማሳድ ቦዉሎስ ጋር ሥለሱዳን ሰላም በድብቅ ተነጋገሩ።-የአዉሮጳ፣ የዩክሬንና የዩናይትድ ስቴትስ መሪዎች ዛሬ በቪዲዮ ያደረጉት ጉባኤ አግባቢ እንደነበር የአዉሮጳ መሪዎች አስታወቁ።ጉባኤዉ የዩናይትድ ስቴትስና የሩሲያ መሪዎች የፊታችን አርብ በሚያደርጉት ጉባኤ የአዉሮጳና የዩክሬን ፍላጎት እንዳይዘነጋ ለማሳሰብ ያለመ ነበር