የኢትዮጵያ ብሔራዊ መልሶ ማቋቋም ኮሚሽን ከ65 ሺህ በላይ የቀድሞ ተዋጊዎች ከህዳር አንስቶ ከኅብረተሰቡ ጋር መቀላቀላቸውን አስታውቋል። በመጠለያ ጣቢያ የሚገኙ ሰዎች በግጭት ወቅት ለተቃጠሉ ቤቶቻቸው ግብር እንድንከፍል ተጠይቀናል ሲሉ ብሶታቸውን ተናገሩ። የህዳሴ ግድብ መጠናቀቁ ከተገለጸ በኋላ ግብጽ የምታነሳው ተቃውሞ ፣አሸከርካሪዎች በተለያዩ አቅጣጫዎች ሲጓዙ ከደኅንነት ችግር አንስቶ እስከ ሕገ ወጥ የኮቴ ክፍያ ድረስ የሚገጥማቸው ፈተናዎች እንዲሁም የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካን ዋና ከተማ ዋሽንግተን ዲሲ ፖሊስ ተግባራዊ ያደረጉት የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ
ዜና መጽሔት የሚመለከታቸው ጉዳዮች ናቸው