Dw Amharic-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ማረቆ ልዩ ወረዳ ዛሬ እኩለ ቀን አካባቢ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ህይወት ማለፉ፣በአማራ ክልል ተገቢ ያልሆነ የዋጋ ጭማሪ አድርገዋል በተባሉ 7ሺህ የሚጠጉ ነጋዴዎች ላይ እርምጃ መውሰዱ፣ አርብ ዕለት በዌስት ባንክ የተገደለችው ቱርካዊ-አሜሪካዊት ወጣት ግድያ በገለልተኛ ወገን እንዲጣራ መጠየቁ፣ሩሲያ በአሜሪካ መገናኛ ብዙሃን ላይ ገደብ እንደምትጥል መግለጿ እንዲሁም የዶናልድ ትራምፕ ክስ የሀገሪቱ ምርጫ እስኪጠናቀቅ ድረስ ብይኑ እንዲዘገይ መወሰኑን የዛሬው የዓለም ዜና የያዛቸው ርዕሰ ጉዳዮች ናቸው።