-ለኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የቀረበዉ «ንብረት የማስመለስ ረቂቅ አዋጅ» ዉጪ በሚኖሩ ኢትዮጵያዉንና ትዉልደ ኢትዮጵያዉያን ላይ ችግር የሚፈጥር ከሆነ ከአዋጁ አርቃቂዎች ጋር እንደሚነጋገርበት የዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ።-ምዕራባዊ ሱዳን ዳርፉር ግዛት ዉስጥ ለረሐብ ለተጋለጠዉ ሕዝብ ተጨማሪ የምግብ ርዳታ ማከፋፈሉን የዓለም ምግብ ድርጅት አስታወቀ።-የእስራኤል ጦር ከደቡብ ጋዛን ከሰሜን ደቡባዊ ሊባኖስን መደብደቡን ዛሬም እንደቀጠለ ነዉ።የሊባኖሱ ደፈጣ ተዋጊ ቡድን ሒዝቡላሕም ሰሜናዊ እስራኤል በሚሳዬል መደብደቡን አስታዉቋል።