ከባለፈው ዓመት ጀምሮ ምሥራቅ ቦረና በሚል አዲስ ዞን ስር የሚተዳደረው ጎሮዶላ ወረዳ እየተጓተተ በሚከፈው ደሞዝ መቸገራቸውን ሠራተኞች አመለከቱ። ሠራተኞቹ እንደሚሉት ከሚያዚያ ወር ወዲህ ደሞዝ አላገኙም።
የየመን ሁቲ አማጽያን ዛሬም በቀይ ባሕር ላይ ስትጓዝ በነበረች በመርከብ ላይ አምስት ሚሳኤል መተኮሳቸው ተነገረ። የብሪታንያ የባሕር ንግድ ኮርፖሬሽን ዛሬ እንደገለጸው በመርከቧ ላይ ጉዳት አልደረሰም።
የአውሮጳ ሕብረት ሃገራት መሪዎች ለሕብረቱን ኮሚሽን ፕሬዝደንትነት ዑርዙላ ፎንደር ሌይንን ለሁለተኛ ጊዜ በይፋ ሰየሙ። ጉባኤው የኢስቶኒያ ጠቅላይ ሚኒስትር ካያ ካሌስንም ለሕብረቱን የውጭ ጉዳይ ኃላፊነት መርጧል።