-የዩናይትድ ስቴትስ መንግስት ኢትዮጵያ ዉስጥ የሚደረገዉን ግጭት ለማስቆም ጠንካራ ርምጃ ይወስድ ዘንድ የኢትዮጵያዉያን አሜሪካዉያን የሲቪል ማሕበራት ምክር ቤት አባላት ጠየቁ።-የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብቶች ኮሚሽንን (ኢሰመኮ)ን ላለፉት አምስት ዓመታት የመሩት ዶክተር ዳንኤል በቀለ ዛሬ ተሰናበቱ።የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ ትናንት በሥም ያልጠቀሷቸዉን የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ወቅሰዉ ነበር።-ትናንት ብሪታንያ ዉስጥ በተደረገዉ ምርጫ ያሸነፈዉ የሐገሪቱ የሠራተኛ ወይም ሌበር ፓርቲ መሪ ዛሬ የጠቅላይ ሚንስትርነቱን ሥልጣን ያዙ።