-ሶማሊያ የሠፈረዉ የኢትዮጵያ ሠራዊት የወደፊት ተልዕኮን የሚመለከት መልዕክት ኢትዮጵያ በይፋ እንዳልደረሳት የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር አስታወቀ።ኢትዮጵያ ከሶማሊላንድ ጋር ያደረገችዉን ዉል ካልሰረዘች የኢትዮጵያ ጦር ከሶማሊያ እንደሚወጣ የሶማሊያ ሁለት ባለሥልጣናት ባለፈዉ ሰኞ አስታዉቀዉ ነበር።-የኢትዮጵያ የሚንስትሮች ምክር ቤት ለመጪዉ የበጀት ዓመት ወደ አንድ ትሪሊዮን ብር መደበ።በሁለተኛዉ የዓለም ጦርነት ወቅት የናትሴ ጀርመንን ድል ያደረጉት የተባባሪ ሐገራት ጦር ኖርማንዴይ ፈረንሳይ የገባበት 80ኛ ዓመት ታሰበ።