የሰኔ 30 ቀን 2017 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኬንያ ፖሊስ ዛሬ ከፀረ-መንግስት ተቃዋሚ ሰልፈኞች ጋር ተጋጨ። ሰልፈኞቹ እሳት አቃጥለዋል ፖሊስ ላይም ድንጋይ ወርውረዋል። ፖሊስም በሰልፈኞቹ ላይ አስለቃሽ ጢስ ተኩሷል።
እስራኤልና ሀማስ የተኩስ አቁም ላይ ለመድረስ ዶሀ ኳታር ውስጥ ቀጥተኛ ያልሆነ ድርድር ቢጀምሩም በቅድመ ሁኔታዎችዎቻቸው ሰበብ በተደጋጋሚ እየተቋረጠ ነው።
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ የብሪክስ ቡድን አባል ለመሆን የሚፈልጉ ሀገራትን በታሪፍ እንደሚቀጡ አሳወቁ ። የብሪክስ አባል ሀገራት የታሪፍ ጭማሪው ለዓለም አቀፉ ንግድ አደጋ ነው ሲሉ አስጠንቅቀዋል።