ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ በአዲስ አበባ ተገናኙ። በኢትዮጵያ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ ከውድቀት አፋፍ እንደሚገኝ መንግሥት እና አራት ድርጅቶች አስጠነቀቁ። በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ሊባባስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባልደረባ ሥጋታቸውን ገለጹ። ስዊድን በኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ በሕይወት እንዳለ ገለጸች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ቋሚ የአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ በዕጣ የሚያገኙበትን የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም ሊያቆም ነው።