የዓለም ዜና

የታኅሳስ 10 ቀን 2018 የዓለም ዜና


Listen Later

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ እና የሶማሊያው ፕሬዝደንት ሐሰን ሼክ ማሕሙድ በአዲስ አበባ ተገናኙ። በኢትዮጵያ ለስደተኞች የሚደረገው ድጋፍ ከውድቀት አፋፍ እንደሚገኝ መንግሥት እና አራት ድርጅቶች አስጠነቀቁ። በአማራ ክልል ያለው ሁኔታ ሊባባስ እንደሚችል የዓለም አቀፉ ቀይ መስቀል ኮሚቴ ባልደረባ ሥጋታቸውን ገለጹ። ስዊድን በኤርትራ ላለፉት 24 ዓመታት በእስር ላይ የሚገኘው ጋዜጠኛ ዳዊት ይስሐቅ በሕይወት እንዳለ ገለጸች። የፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ኢትዮጵያውያንን ጨምሮ የሌሎች ሀገር ዜጎች ቋሚ የአሜሪካ የመኖሪያ ፈቃድ በዕጣ የሚያገኙበትን የዲቪ ሎተሪ ፕሮግራም ሊያቆም ነው።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW