-ኢትዮጵያ የሶማሊያን ሠላም ለማስከበር አዲስ ተልዕኮ ከተቀበለዉ የአፍሪቃ ሕብረት ሠራዊት ጋር እንደምትተባበር አስታወቀች።የኢትዮጵያ ዉጪ ጉዳይ ሚንስቴር የኢትዮጵያን ዕቅድ ይፋ ያደረገዉ የኢትዮጵያ መከላከያ ሚንስትር ከሶማሊያ ፕሬዝድንትና ከሌሎች ባለሥልጣናት ጋር ትናንት ከተነጋገሩ በኋላ።----ኢትዮጵያ ዉስጥ የአፋር ክልልን በተከታታይ የመታዉ የመሬት መንቀጥቀጥ እሳተ ጎሞራ ሳያፈነዳ እንዳልቀረ ተነገረ።-----ጀርመንና ፈረንሳይ ለአዲሶቹ የሶሪያ ባለሥልጣናት ድጋፍ እንደሚሰጡ የሁለቱ ሐገራት ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች አስታወቁ።ሁለቱ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ደማስቆ ዉስጥ ከአዳዲሶቹ የሶሪያ መሪዎች ጋር ተነጋግረዋል።ዜናዉ በዝርዝር።