-በደቡብ ኢትዮጵያ ኮሬ ዞን፣ ጎርካ ወረዳ ታጣቂዎች ሁለት ገበሬዎችን በጥይት ደብደዉ፣ በገጀራ ተልትለዉ ገደሉ።የኮሬ ዞን ባለሥልጣናት ገዳዮቹን ከአጎራባች ወረዳ የገቡ «ፀረ-ሠላም» ኃይላት ብለዋቸዋል።በዞኑ ታጣቂዎች በተደጋጋሚ ሰላማዊ ሰዎችን ይገድላሉ።-----ዩናይትድ ስቴትስ የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ሠራዊት አዛዥ ጄኔራል መሐመድ ሐምዳን ዳግሎ (ሕምዲቲ)ና ቤተሰቦቻቸዉ አሜሪካ እንዳይገቡ አገደች---የዩናይትድ ስቴትስ ተመራጭ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ የፓናማ ቦይን፣የዴንማርክን ግሪንላንድንና ካናዳን በኃይል ጭምር ለመያዝ መዛታቸዉ የአዉሮጳና የአሜሪካ መንግሥታትን አስደግጧል።