የኢትዮጵያ መንግሥት ኃይለማርያም ደሳለኝ ሥልጣን ላይ ሳሉ የተሸጠው ቦንድ ወለድ ከ6.625 ወደ 5.5 በመቶ ዝቅ እንዲል ይፈልጋል። ከዚህ በተጨማሪ በሚቀጥለው ዓመት የሚጎመራው ቦንድ የሚከፈልበት ጊዜ እንዲሸጋሸግ ይሻል። የኢትዮጵያ ቦንድ ባለቤቶች እና የገንዘብ ሚኒስቴር ባለሥልጣናት ነገ ለመነጋገር ቀጠሮ አላቸው። ቀጠሮው ኢትዮጵያ 33 ሚሊዮን ዶላር ወለድ እንደማትከፍል ካሳወቀች በኋላ የተያዘ ነው።