የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በቅርቡ ይፋ ባደረገው ሰነድ የክልል መንግሥታት እና የከተማ መስተዳድሮች ቦንድ በማውጣት ከገበያው የሚበደሩበት ሥርዓት የመዘርጋት ፍላጎት እንዳለው ፍንጭ ሰጥቷል። የማዘጋጃ ቤት ወይም የከተማ አስተዳደር ቦንዶች ለመሠረተ-ልማት ግንባታ የሚያስፈልግ ገንዘብ ለመበደር የሚያገለግሉ ናቸው። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እና የሲዳማ ክልል በቁልፍ የልማት ዘርፎች ረገድ ያለባቸውን የገንዘብ እጥረት ለመቅረፍ ቦንድ በማውጣት ከገበያው የመበደር ፍላጎት እንዳላቸው የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በቅርቡ ይፋ ያደረገው አንድ ጥናት አሳይቷል።