በ2017 የኢትዮጵያ የበጀት ጉድለት ከአጠቃላይ ሀገራዊ የምርት መጠን 2.1% ድርሻ እንደሚኖረው አቶ አሕመድ ሽዴ ተናግረዋል። መንግሥት ለሚቀጥለው ዓመት ያዘጋጀው 971 ቢሊዮን ብር በጀት 358.5 ቢሊዮን ብር ጉድለት ይገጥመዋል። ከ2017 በጀት 139.3 ቢሊዮን ብር ለዕዳ ክፍያ የታቀደ ነው። መንግሥት ኤኮኖሚው በ8.4% ያድጋል ብሎ ይጠብቃል። ኢትዮጵያ የምትከተለው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ሥርዓት በ2017 እንደሚቀጥል የገንዘብ ሚኒስትሩ አቶ አሕመድ ሽዴ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ገልጸዋል።