የዓለም ዜና

የጥቅምት 08 ቀን 2018 የዓለም ዜና


Listen Later

በኪሱሙ የራይላ ኦዲንጋ መታሰቢያ ዝግጅት ላይ በርካታ ሰዎች መቁሰላቸውን የኬንያ ቀይ መስቀል ባለሥልጣናት ተናገሩ። የፈረንሳዩ ቢኤንፒ ፓሪስባስ ዩናይትድ ስቴትስ ሱዳን ላይ የጣለችውን ማዕቀብ በመተላለፍ በሰጠው የባንክ አገልግሎት የኦማር አል-በሽር መንግሥት የዘር ማጥፋት እንዲፈጽም ረድቷል በሚል በአሜሪካ ፍርድ ቤት ጥፋተኛ ተባለ። በእስራኤል እና በሐማስ ጦርነት የተገደሉ ፍልስጤማውያን ቁጥር ከ68,000 በላይ መድረሱን የጋዛ የጤና ሚኒስቴር ዛሬ ቅዳሜ አስታወቀ። ኢራን ከአስር ዓመታት በፊት በኑክሌር መርሐ-ግብሯ ላይ ከልዕለ-ኃያላኑ የተፈራረመችው ሥምምነት በማብቃቱ በውሉ በተካተቱ ገደቦች እንደማትገዛ አስታወቀች።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW