የሰዎች ከቦታ ቦታ የመንቀሳቀስ መብት አሳሳቢ በሆነ ሁኔታ እየተጣሰ ነው ሲል የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) አመለከተ፡፡ እስራኤል ዛሬ በደቡብ ሊባኖስ በፈጸመችው «መጠነ ሰፊ» የተባለለት የአየር ጥቃት 1 ሰው ሲገደል 7 መቁሰላቸውን የሐገሪቱ የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ። ጓቲማላ ከዩናይትድ ስቴትስ የተባረሩ የመጀመሪያው ዙር ስደተኞች ተቀበለች። ስደተኞቹ የራሷ እና የሁንድራስ መሆናቸውን ታውቋል። የሰብአዊ መብት ተከራካሪዎች ድርጊቱን አውግዘዋል።