ትናንት ማምሻውን በአዲስ አበባ መርካቶ የተነሳውና ለረዥም ሰዓት የቆየው የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ከባድ ጉዳት ሳያደርስ እንዳልቀረ እየተነገረ ነው። እሳቱ እስከ ዛሬ ማለዳ ድረስ ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥር ሥር አልዋለም ነበር። መስኤውም እልታወቀም።
ከአንድ ወር በላይ ተዘግቶ የቆየው የኢትዮ ሱዳን ደንበር ከትናንት አንስቶ ጀምሮ እንደገና ተከፍቶ አገልግሎት መጀመሩን የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳደር አስታወቀ።
የሱዳን ጦር ባካሄደው የአየር ጥቃት ቢያንስ 31 ሰዎች መገደላቸውን የአካባቢው የመብት ተሟጋቾች አስታወቁ።
የአውሮጳ ዓርላማ ከታገደው የሩሲያ ንብረት ላይ ለዩክሬን 35 ቢሊየን ዩሮ ብድር አጸደቀ።