የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለሥልጣን ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ የዶቼ ቬለ ዘጋቢዎችን ለጊዜው ማገዱን በዛሬው ዕለት በደብዳቤ አስታወቀ።
ከሁለት ዓመት በላይ በዘለቀው የሱዳን ጦርነት ሕዝቡ አሳሳቢ የሰብአዊ ቀውስ እየተጋፈጠ እንደሚገኝ የተመ የሕጻናት መርጃ ድርጅት ዩኒሴፍ አመለከተ።
በመላው ዓለም ከሚካሄዱት ግጭቶች 40 በመቶው አፍሪቃ ውስጥ እንደሆነ ዓለም አቀፉ የቀይ መስቀል ኮሚቴ ገለጸ።
የአውሮጳ ሕብረት በዛሬው ዕለት ሩሲያ ላይ ተጨማሪ ማዕቀቦችን ጣለ።