የዓለም ዜና

የጥቅምት 20 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና


Listen Later

በዎላይታ ዞን እና በሲዳማ ክልል ውስጥ ትናንት በደረሰ መሬት መንሸራተት የዘጠኝ ሰዎች ሕይወት አለፈ። የአደጋው መንስኤ በሌሊት የጣለው ከባድ ዝናብ እንደሆነ ተገልጿል።
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ጉራጌ ዞን በፀጥታ አባላት የጅምላ እሥር እየተፈጸመ መሆኑን የአካባቢው ነዋሪዎች አመለከቱ። መንስኤው ከሸኔ አለያም ከፋኖ ጋር ግንኙነት አላችሁ የሚል ነው ተብሏል።
የሴኔጋል ባሕር ኃይል ባለፉት 10 ቀናት 600 የሚሆኑ ሕገወጥ ስደተኞችን ከባሕር ላይ መያዙን አስታወቀ።
ኢራን በእስራኤል ጥቃት የሚሳኤል ማምረቻዎቼ አልተጎዱም አለች።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW