የጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም. አርዕስተ ዜና
የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ ዜጎች «የአካባቢያቸውን ልማት ማገዝ እንዲችሉ ሰላም ያስፈልጋል» ሲሉ ዛሬ ተናገሩ።
የሱዳን ጦር፣የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል ለሊቱን በሰሜን ምሥራቅ ሱዳን ሁለት ከተሞች ላይ የጣላቸውን የድሮኖች ጥቃቶች መመከቱን አስታወቀ። የጥቃት ዒላማ የአትባራ ከተማና ሪቨር ናይል ክፍለ ሀገር ናቸው።
ከበርካታ የአፍሪቃ ሀገራት የመጡ ከ1400 በላይ አፍሪቃውያን ከሩስያ ኅይሎች ጎን ተሰልፈው ይዋጋሉ ስትል ኪቭ አስታወቀች።