የዓለም ዜና

የጥር 12 ቀን 2017 ዓ.ም. የዓለም ዜና


Listen Later

በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መንዝ ላሎ ምድር ወረዳ የሚገኙ መምህራንና ሌሎች ሠራተኞች ለአራት ወራት ደመወዝ እንዳላገኙ አመለከቱ። የወረዳው የመንግሥት ኮሚኖኬሽን ጉዳዮች ጽ/ቤት በወረዳው 1300 የሚሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ለችግር መጋለጣቸውን ገልጿል።
ኦክስፋም የተሰኘው የረድኤት ድርጅት የቢሊየነሮች ሀብት በፍጥነት እያደገ ሊሄድ ይችላል አለ። ድርጅቱ እንደሚለው ከዓለም ሀብት 45 በመቶ የሚሆነው ከዓለም ሕዝብ አንድ በመቶ ብቻ በሚሆኑት ቱጃሮች እጅ ነው።
የዩናይትድ ስቴትስ ተመራጭ ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ በዛሬው ዕለት ቃለመሐላ በመፈጸም በይፋ ሥራቸውን እንደሚጀምሩ እየተጠበቀ ነው።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW