-የደቡብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የቤንዚን እጥረትና ሽያጭን ለመቆጣጠር በክልሉ ቤንዚን በኩፖንና በቁነና እንዲሸጥ ወሰነ።የኢትዮጵያ መንግስት በነዳጅ ዘይት ዋጋ ላይ በተደጋጋሚ የጣለዉ የዋጋ ጭማሪና የተከሰተዉ እጥረት የአብዛኛዉን ኢትዮጵያዊ ኑሮና እንቅስቃሴ እያወከ ነዉ።---ኢትዮጵያዉያን ስደተኞችን አሳፍራ ከጅቡቲ ወደ የመን ትቀዝፍ የነበረች አንዲት አነስተኛ ጀልባ ተገልብጣ 20 ኢትዮጵያዉያን ስደተኞች ሞቱ።---የአዲሱ የዩናትድ ስቴትስ ፕሬዝደንት የዶናልድ ትራምፕ መርሕ ያሰጋቸዉ የአዉሮጳ መሪዎች መፍትሔ ፍለጋ እየባተሉ ነዉ።