ዶይቼ ቬለ ፈቃዳቸው የተሰረዘ ሁለት ዘጋቢዎቹን ዕጣ ፈንታ በተመለከተ ለኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጥያቄ አቀረበ።
የዩጋንዳ ፕሬዝደንት ልጅ የሆኑት የሀገሪቱ ጦር ኃይል ኃላፊ ከምርጫ ጋር በተያያዘ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ 30 ሰዎች መገደላቸውን፤ ከሁለት ሺህ በላይ ደግሞ መታሠራቸውን አስታወቁ። የተመድ የዩጋንዳ ወቅታዊ ሁኔታ እንዳሳሰበው ገልጿል።
ኢራን ውስጥ ከአምስት ሺህ በላይ ተቃዋሚዎች በመንግሥት የፀጥታ ኃይሎች መገደላቸውን የመብት ተሟጋቾች አመለከቱ።
ዳቮስ ስዊዝርላንድ በተካሄደው የዓለም የኤኮኖሚ ጉባኤ አሳሳቢ የዓለም ችግሮች ችላ ተብለዋል ተባለ።