የኢትዮጵያ ብሔራዊ መረጃ እና ደሕንነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ሆነው በመሥራት ላይ የነበሩት አቶ ተመስገን ጥሩነሕ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር፤ ታዬ አጽቀሥላሴ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር፤ ዶክተር መቅደስ ዳባ የጤና ሚኒስትር ሆነው ተሾሙ። የኦሮሞ ነጻነት ግንባር የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ መንግሥት ከአምስት ዓመታት ገደማ በፊት በኤርትራ ዋና ከተማ አስመራ የተፈረመውን ሥምምነት አፍርሷል ሲል ከሰሰ። ከቱኒያዝ የባሕር ዳርቻ ጀልባ ሰጥማ ሕይወታቸውን ያጡ 13 ሱዳናውያን አስከሬን ተገኘ። ጠቅላይ ሚኒስትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ የእስራኤል ወታደሮች በጋዛ ወደምትገኘው ራፋ ለመግባት እንዲዘጋጁ ትዕዛዝ ሰጡ።