የዓለም ዜና

የጥር 30 ቀን 2017 ዓ.ም የዓለም ዜና


Listen Later

አርስተ ዜና፤
-በዴሞክራቲክ ኮንጎ ጦር እና በሩዋንዳ ይደገፋል በሚባለው የM 23 አማጺዎች መካከል ውጊያው መባባሱ ተነገረ። ኮንጎ በሲቪሎች ላይ ለደረሰው ግድያ እና አስከፊ የሰብአዊ መብቶች ጥሰት የተመድ ሩዋንዳን ተጠያቂ ያድርግልኝ ብላለች። --በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን መኪና በማስቆም በተደረገ እገታ አንድ ሰው ተገደለ፤ አራት ደግሞ መቁሰላቸውን የዓይን እማኝ ተናገሩ።--የአሜሪካው ፕሬዝደንት ዶናልድ ትራምፕ ዓለም አቀፉ የጦር ወንጀል ተመልካች ፍርድ ቤት ላይ የጣሉትን እገዳ በርካታ ሃገራት ተቃወሙ። ትራምፕ የICCን ንብረት በማገድ፤ ባለሥልጣናቱ፣ ሠራተኞቹ እና ቤተሰቦቻቸው ላይ የጉዞ እገዳ ጥለዋል።
...more
View all episodesView all episodes
Download on the App Store

የዓለም ዜናBy DW