-የአፋር ክልልን በመታዉ የመሬት መንቀጥቀጥ አደጋ ከቤት ንብረታቸዉ የተፈናቀሉ ሰዎች በቂ ዕርዳታ እንዳላገኙ አስታወቁ።በመሬት መንቀጥቀጡ ከተጎዱ አካባቢዎች ከ60 ሺሕ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል።ተፈናቃዮቹና ርዳታ አቀባዮች እንደሚሉት የምግብ፣የመድሐኒትና የመጠለያ ድጋፍ ያስፈልጋቸዋል።----የሶማሊያ የፀጥታ ኃይላት በሐገሪቱ ሰሜናዊ ግዛት ሸምቀዉ ነበር ያሏቸዉን የእስላማዊ መንግስት (IS) ታጣቂዎች መግደላቸዉን አስታወቁ።-የእስራኤልና የሐማስ ተደራዳሪዎች ጋዛን የሚያወድመዉን ጥቃት ለማቆምና ታጋቾችን ለመልቀቅ የሚረዳ ስምምነት ለማድረግ መቃረባቸዉ እየተነገረ ነዉ።