የዜና መፅሔት ዝግጅታችን፣ ወታደራዊ ንቅናቄ በሰሜን ኢትዮጵያ፤ የኢትዮጵያ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአቪሽን ፀጥታ ላይ ያደረገዉን ዉይይት። የበኒ ሻንጉል ጉሙዝ ክልል ባለፉት 6 ወራት ከ41 ኩንታል በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማስገባቱን አስታዉቋል።አርባ ምንጭ ዙሪያ ወረዳ 15 ሰዎች መገደላቸዉ ተዘግቧል።የኦሮሚያ ክልል ምክር ቤት (ጨፌ ኦሮሚያ) በክክሉ ፀጥታና የኑሮ ዉድነት ላይ ያደረገዉ ዉይይት ሌላዉ የዜና መፅሔት ርዕሳችን ነዉ። ዜና መፅሔቱ ደቡብ ወሎ ዞን 276 ሺሕ ተማሪዎች ትምሕርት ማቋረጣቸዉን ይቃኛል። ሳምንታዊ ጤናና አካባቢ ምዕራብ ሸዋ ዉስጥ ምንነቱ በዉል ያልታወቀ አዉሬ ያደረሰዉን ጥቃት ይዳስሳል።