-ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ (ህወሓት) የተመሠረተበት 50ኛ ዓመት ለሁለት ከተከፈሉት የፓርቲዉ አንጃዎች በአንደኛዉ መቀሌ ዉስጥ ተከበረ።ጠቅላይ ሚንስትር ዓብይ አሕመድ በዓሉን ምክንያት በማድረግ መልዕክት አስተላልፈዋል።----የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ጦር በሁለት የደቡባዊ ሱዳን መንደሮች በከፈተዉ ጥቃት በትንሹ 200 ሠላማዊ ሰዎች መግደሉን አንድ የመብት ተሟጋች ቡድን አስታወቀ።----የሩሲያና የዩናይትድ ስቴትስ ዉጪ ጉዳይ ሚንስትሮች ሪያድ-ሳዑዲ አረቢያ ዉስጥ ባደረጉት ዉይይት የዩክሬኑ ጦርነት እንዲያበቃ የሚደራደር የባለሥልጣናት ቡድን ለመሰየምና የአሜሪካና የሩሲያ ግንኙነትን ለማሻሻል ተስማሙ።