-የኢትዮጵያ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሐገሪቱን ብሔራዊ የምክክር ኮሚሽን የሥራ ዘመንን ለተጨማሪ 8 ወራት አራዘመ።-የቱርክ ፕሬዝደንት ሬሰፕ ጠይብ ኤርዶኻን የአፍሪቃ ቀንድ መንግሥታት ሉዓላዊነትና የግዛት አንድነት መከበር እንዳለበት አሳሰቡ።ኤርዶኻን አዲስ አበባ ዉስጥ ከጠቅላይ ሚንስትር አብይ አሕመድ ጋር ከተወያዩ በኋላ እንዳሉት የአፍሪቃ ቀንድ ተጨማሪ ግጭትና መከራ ሊደርስበት አይገባም።-የሩሲያና የዩክሬን ተደ,ራዳሪዎች ዤኔቭ-ስዊዘርላንድ ዉስጥ ያደረጉት ድርድር ያለዉጤት አበቃ።የሁለቱ ሐገራት ባለሥልጣናት ያደረጉትን ድርድር የሸመገሉት የዩናይትድ ስቴትስ ባለሥልጣናት ናቸዉ።