• የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት ትግራይ ክልል ውስጥ ወደ ሚገኙ የቀድሞ የጦር ሰፈሮቹ ይገባል ተብሎ የተሰራጨው መረጃ «ሐሰት ነው » ሲል የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር አስተባበለ።
• እስራኤል በሊባኖስ ምስራቃዊ ክፍል በሚገኘው የበካ ሸለቆ በፈጸመችው የአየር ጥቃት ሦስት ሕጻናትን ጨምሮ ቢያንስ 10 ሰዎች መገደላቸውን የሀገሪቱ ጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።
• ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ወደ አሜሪካ በሚገቡ ሁሉም ምርቶች ላይ ተጨማሪ የ10 በመቶ ቀረጥ ጣሉ ።
• ዩክሬን ሩስያ ውስጥ ጠልቃ በመግባት በፈጸመችው የድሮን ጥቃት በሚሳኤል ማምረቻ ኢንዱስትሪ ላይ ጉዳት ማድረሷ ተነገረ። በጥቃቱ 11 ሰዎች ቆስለዋል።